DW Amharic Profile Banner
DW Amharic Profile
DW Amharic

@dw_amharic

Followers
151,235
Following
0
Media
3,311
Statuses
11,743

ዶይቸ ቬለ በራዲዮ በኢንተርኔት ዜና፣ ትንታኔ ከጀርመን በ 31 ቋንቋዎች ያሰራጫል። እባክዎ የኢንተርኔት ደንባችንን ያስተውሉ። ቦን፣ ጀርመን Telegram:

Bonn, Germany
Joined July 2010
Don't wanna be here? Send us removal request.
Explore trending content on Musk Viewer
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በጥቅምት ወር ኃይል ማመንጨት ይጀምራል ተባለ።
Tweet media one
30
406
1K
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት በአንድ ወገን ትርክት ላይ ከተመሰረቱ ውሳኔዎች ሊወጣ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ለፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ ገለጹ።
Tweet media one
28
434
965
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ምስራቅ ወለጋ ኪራሙ ወረዳ የሸኔ ታጣቂ የተባሉ ከ200 በላይ ሰዎች ገደሉ፣40 ሺሕ አፈናቀሉ።የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ታጣቂዎቹ ካለፈዉ ሮብ ጀምሮ 6 ቀበሌዎችን ወርረዉ የአማራ ተወላጆን በጥይትና በገጀራ ገድለዋቸዋል። ባለስልጣናት ስልክ አያነሱም
Tweet media one
133
503
570
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ኢትዮጵያውያን፦ የምዕራባውያን ጣልቃ ገብነትን በመቃወም #NoMore (በቃ) በሚል የጀመሩት ንቅናቄ ሌሎች አፍሪቃውያንንም ያነቃቃ መስሏል። በትዊተር «ፊውቹሪካል» በሚል ስማቸው የሚታወቁት ዩጋንዳዊ በንቅናቄው ንቁ ተሳታፊ ናቸው።
Tweet media one
35
177
512
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
በሕወሓት ኃይሎች ቁጥጥር ስር የነበረችውን የውጫሌ ከተማ የመንግስት ወታደሮች እና አጋሮች ትናንት ሰኞ መቆጣጠራቸውን የአካባቢው ነዋሪ ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ።
Tweet media one
33
143
459
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
በትግራይ ክልል ላይ የተጣሉ ዕቀባዎች ከተነሱ እና የተቋረጡ አገልግሎቶች ከተመለሱ ሕወሓት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ለመደራደር ፍቃደኛ መሆኑን የግንባሩ ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ ።
Tweet media one
437
133
444
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ የህዳሴ ግድብ በቅርቡ የሙከራ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር ተነገረ።
Tweet media one
Tweet media two
35
91
435
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
በመላው ዓለም የሚገኙ የኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ምዕመናን ጾመ ነነዌን ጥቁር ልብስ በመልበስ የጸሎት መርሐ ግብሮችን እየተካፈሉ ነዉ።
Tweet media one
16
118
401
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
አምባገነኖችን ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳቸው ምን እንደኾነ ታውቃላችሁ? አድሏዊ ላልኾነ ጋዜጠኝነት ቊርጠኛ መኾናችን ለመናገር ነፃነትና በዓለም ዙሪያ ከ180 በሚበልጡ ሃገራት ዲሞክራሲያዊ እሴቶች እንዲጎለብቱ ይረዳል።
21
22
372
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ግዕዝ ቋንቋ በስርዓተ ትምህርት ሊካተት ነው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ መድረክ ቀደምት አባቶችን መፅሐፍት ለመረዳት ግዕዝን በትምህርት ስርዓት አካትቶ ማስተማር አስፈላጊ ነው ተብሎአል።
Tweet media one
17
91
298
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
«ፍትኅ ለአዲስ አበባ» በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ ስለ አዲስ አበባ ፍትኅ የሚጠይቅ የማኅበራዊ መገኛ ዘዴዎች ዘመቻ ዛሬ በዋናነት በትዊተር ላይ ተጀመረ። ዘመቻው ነገም እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ ገልጠዋል።
Tweet media one
22
101
301
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የፍትሕ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ዕለት ታስሮ በሚገኝበት ፖሊስ ጣቢያ ድብደባ ተፈጸመበት።
Tweet media one
43
157
272
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
በምስራቅ ወለጋ እና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚፈፀመውን ጥቃት በአስቸኳይ ማስቆም እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ኢዜማ ጠየቀ።
Tweet media one
24
114
261
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የሕወሓት ተዋጊዎች ጭናና ቆቦ ከተሞችን ተቆጣጥረዉ በነበረበት ወቅት በርካታ ሰዎች መግደላቸዉንና ሴቶችን መድፈራቸዉን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አጋለጠ። የመብት ተሟጋቹ ድርጅት ዛሬ እንዳመለከተዉ ታጣቂቹ የ14 ዓመት ልጃገረድን ሳይቀር ደፍረዋል።
Tweet media one
22
173
245
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የኢትዮጵያ የጦር ጄቶች ማምሻዉን መቀሌ አካባቢን መደብደባቸዉን የትግራይ መንግስት አስታወቀ።የክልሉ የኮሙኒኬሽን ቢሮ፣ጄቶቹ ቦምብ ጣሉ ከማለት ባለፍ ትክክለኛዉን ሥፍራና ጉዳቱን አልጠቀሰም።ጥቃቱን«የትግራይ ሕዝብን ለማንበርከክ» ያለመ ብሎታል
Tweet media one
58
81
236
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
እንኳን ደስ አለሽ ጡሩዬ !
Tweet media one
10
15
229
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ባወጣው የአቋም መግለጫ በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ለተፈጸመው ዘግናኝ ግድያ የመንግስት አመራር በከፊል ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኑን ገለጠ። ለዝርዝሩ
Tweet media one
30
98
226
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የእስራኤል የህክምና እና የፓርላማ ባለሥልጣናት በጦርነቱ የተጎዱ ሀኪም ቤቶችን እና የተጎዱ ሰላማዊ ሰዎችን ለመርዳት ኢትዮጵያ ገብገዋል።
Tweet media one
22
65
223
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ብሪታንያ ከኢትዮጵያ የተዘረፉ ቅርሶችን መለሰች ለንደን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዛሬ እንዳስታወቀው የተመለሱት ቅርሶች ከ150 ዓመታት በፊት ከመቅደላ የተዘረፉ ናቸው።
Tweet media one
6
81
204
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ታዋቂው የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል እና የኦክላሆማ ግዛት ሴናተር ጂም ኢንሆፍ በፕሬዚደንት ጆ ባይደን የሚመራው የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ኢትዮጵያ ላይ የጣለውን ማእቀብ እንደሚቃወሙ ገለጡ።
Tweet media one
5
64
214
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የኢትዮጵያ መንግስት ከሕወሓት ጋር አለመነጋገሩን አስታቀ።ሕወሓት ከመንግስት ጋር መደራደሩን ሊቀመንበር ደ��ረፅዮን አስታዉቀዉ ነበር።የኮሙኑኬሽን ሚንስትር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለዶቸ ቬለ እንደነገሩት ግን ከሕወሓት ጋር የተደረገ ንግግር የለም።
Tweet media one
50
84
218
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
የጀርመኑ ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ከDW የአማርኛው ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ-መጠየቅ «ኢትዮጵያዉያን በጀመሩት መንገድ እንዲቀጥሉ እናበረታታለን» ብለዋል። ሙሉ ቃለ ምልልሱን ለማድመጥ/ለማንበብ ይህን ይጫኑ 👉
7
25
206
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦ.ፌ.ኮ) በዘንድሮው 6ኛ ብሔራዊ ምርጫ እንደማይወዳደር ውሳኔ ላይ መድረሱን አሳወቀ። የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ይህን ለዶይቼ ቬለ ዛሬ አረጋግጠዋል።
Tweet media one
26
75
196
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የኢትዮጵያ መንግስት ባለፈዉ ሰኔ 11 ወለጋ፣ ቶሌ ቀበሌ ቀበሌዎች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 338 ናቸዉ ማለቱ፣ተቃዉሞ፣ ጥያቄ እየተሰነዘረበት ነዉ።ዘመድ ወዳጆቻቸዉ የተገደሉባቸዉ፣እንዳስታወቁት የሟቾቹ ቁጥር ከ2 ሺሕ ቢበልጥ እንጂ አያንስም።
Tweet media one
37
110
200
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ምዕራብ ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጸመውን «አሰቃቂ» የጅምላ ግድያ ላይ ባለሥልጣናት ፈጣን፣ ገለልተኛ እና ጥልቅ ምርመራ እንዲያካሂዱ ጠየቀ።
Tweet media one
25
110
203
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
በመንዙማ ስራዎቹ ጎልቶ የሚታወቀው መሐመድ አወል ሳላህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። በሙዚቃ በተለይም «ሰንደል ገላ ገላ » የሙዚቃ ስራውን ጨምሮ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፉለትን በርካታ የነሺዳ ስራዎችን አበርክቷል።
Tweet media one
21
21
195
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ኢትዮጵያዊት አትሌት ለተሰንበት ግዴይ ለሁለት ቀናት ብቻ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን ሰበረች። ለተሰንበት ርቀቱን ያጠናቀቀችዉ በ29 ደቂቃ፣ ከ01 ሴኮንድ፣ ከ03 ሜትሪክ ሴኮንድ ነዉ።
Tweet media one
7
21
188
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ለ11 ዓመታት በየወሩ የ1000 ብር ቦንድ የገዙት ጡረተኛ «ምናልባት ግድቡ ሳያልቅ ባልፍ እንኳ፤ ልጆቼ የገባሁትን ቃል ጠብቀው እስከመጨረሻው የቦንድ ግዥውን እንዲፈፅሙ ተስማምተን ነበር።»
Tweet media one
3
46
198
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ በተካሄደው የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር በኬንያዊው ዳንኤል ኮመን ለ25 አመታት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን አሻሻለ።
Tweet media one
5
30
188
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
"ላለፉት 65 ዓመታት ከ10 ሺህ በላይ ሥዕሎችን የሰሩት" ለማ ጉያ በ92 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከ5 አመታት በፊት የክብር ዶክትሬት ሸልሟቸዋል።
Tweet media one
14
17
178
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
«ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መገኛ ናት። የመጀመሪያው ሆሞ ሴፒያን የፈለሰው ከእርስዎ [ጠ/ሚ ዐቢይ] ግዛት ነው። በዚህም እኛ ሁላችንም ኢትዮጵያውያኖች ነን።» የኖቤል ኮሚቴ ሊቀ መንበር ቤሪት ራይስ አንደርሰን። ሞቅ ያለ ጭብጨባ ከአዳራሹ! #Ethiopia
Tweet media one
6
27
177
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
«እስካሁን በተገኘው መረጃ መሠረት ከ70 እስከ 80 የሚሆኑ ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል» የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ
17
99
171
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የኦሮምያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የሁለት ቀናት ዝግ ጉባዔዉን ሲያጠናቅቅ ዛሬ ምሽት በሰጠዉ መግለጫ አቶ ለማ መገርሳን፤ ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋን እና ወ/ሮ ጠይባ ሀሰንን ከፓርቲዉ ማገዱን አስታወቀ።
Tweet media one
Tweet media two
Tweet media three
47
41
160
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የኦሮሞ መብት ተሟጋቹ ጃዋር መሀመድን በመቃወም ዛሬ በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አደባባይ የወጡት ኢትዮጵያውያን በቅርቡ በሀገሪቱ ለሞቱት 86 ሰዎችም የሻማ ማብራት ስነ ስርዓት አድርገዋል። ጃዋርም ለፍርድ ይቅረብ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
Tweet media one
21
25
167
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
መንግሥት የንፁኃንን መታደግ ባለመቻሉ የተለያዩ ወቀሳዎች እየደረሰበት ነዉ። መንግሥት አሁንም አካባቢዉ ላይ ህግ እንዲያስከብር ለንጹኃን ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል። ለመንግሥት የሚያስተላልፉትን መልዕክት ይጻፉልን!
Tweet media one
88
56
165
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ስለታገቱት ተማሪዎች ዝም አንልም! የታገቱ የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲለቀቁ የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች እየተካሄዱ ነዉ።ሰልፈኞች ተማሪዎቹ የት ናቸዉ?እህት ወንድሞቻችንን መልሱ! ፎቶ፦ የደብረማርቆስ ነዋሪ
Tweet media one
Tweet media two
Tweet media three
Tweet media four
6
39
158
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዛሬ ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት የሚዘልቅ የምህላ ፀሎት አወጀች ።የምህላ ፀሎቱ ዓላማ በሀገሪቱ እየታዬ ያለው ችግር እንዲፈታ ህዝበ ክርስቲያኑ አምላኩን በፀሎት እንዲማፀን ለማድረግ ነው።
Tweet media one
4
20
154
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና ህወሓት "በአፋጣኝ ተኩስ እንዲያቆሙ፤ ዘላቂ ሰላማዊ መፍትሔ ለማበጀት ፖለቲካዊ ልዩነቶቻቸውን በአገሪቱ ሕገ-መንግሥት መሠረት በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲፈቱ የአውሮፓ ምክር ቤት ጠይቋል
39
32
142
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
አዲሱ የሲዳማ ክልል በመጪው ሳምንት ለሚካሄደው የክልላዊ መንግስት መስረታ አስፈላጊውን መሰናዶ ማጠናቀቁን የሲዳማ የክልል ምስረታ ዝግጅት ጽህፈት ቤት አስታወቀ
Tweet media one
10
12
152
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የኢትዮጵያ መንግሥትና ህወሓትን ለማሸማገል ሶስት የቀድሞ መሪዎች አዲስ አበባ ሊጓዙ ነው። ሽማግሌዎቹን የመረጡት የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር ፕሬዝዳንት ራማፎሳ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ ሽምግልናውን ተቀብለዋል ብለዋል👇
Tweet media one
97
22
146
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ይኽ ምስል የተኝቶ ታካሚዎችን ለመጠየቅ ወደ ሀዋሳ አዳሬ ሆስፒታል ግቢ ለመግባት የሚጠባበቁ ሰዎችን ያሳየናል። ስለ ኮሮና ተሐዋሲ ኅብረተሰቡን ግንዛቤ ማስጨበጡ ላይ የሚቀሩ ሥራዎች ያሉ አይመስላችሁም ? ፎቶ፦ ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ ከሀዋሳ (DW)
Tweet media one
23
29
151
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ሰበር ዜና የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የመከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊ ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ከኃላፊነታቸው ተነሱ
Tweet media one
39
18
147
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አንዋር መስጂድ የጁምዓ ሶላት ለመስገድ በሄዱ ዜጎች ላይ የመንግሥት የፀጥታ አካላት በወሰዱት የኃይል ርምጃ የሞት እና የመቁሰል አደጋ መድረሱ ታወቀ። ዝርዝሩ፦
Tweet media one
Tweet media two
Tweet media three
Tweet media four
12
61
151
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ወደ ትግራዊ ሰብዓዊ ርዳታ ጭነው የገቡ 872 ተሽከርካሪዎችን መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጀው ህወሃት ለጦርነት እየተጠቀመባቸው መሆኑን አመለከተ።
Tweet media one
6
79
141
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ዛዲግ አብርሃ «ምዕራባዉያን ስሩ እስኪሉን የምንጠብቅበት ጊዜ አልፎአል። ኢትዮጵያዉያን ከምንጊዜዉም በላይ አሁን ደስተኞች ናቸዉ።»
18
9
144
@dw_amharic
DW Amharic
6 years
ከእስር በቅርቡ የተለቀቀው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የራሱን መጽሔት እና የኢንተርኔት ቴሌቭዥን ሊከፍት ነው። ሥራውን የሚከውንበት ቢሮ የከፈተው እስክንድር በአክሲዮን የሚቋቋም የሳተላይት የቴሌቪዥን ጣቢያ ለመመስረትም እንቅስቃሴ ጀምሬለሁ ብሏል።
Tweet media one
5
24
140
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
የኤርትራ ወታደሮች አሁንም በኢሮብ ወረዳ አካባቢዎች ይገኛሉ። ነዋሪዎቹ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና መሠረታዊ አገልግሎቶች እያገኘን አይደለም ብለዋል። አስተያየቶን ይጻፉልን!
Tweet media one
39
144
131
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ሰሜን ኢትዮጵያ በሚደረገዉ ጦርነት የተካፈሉ ወገኖች በሙሉ በሰብአዊነት ላይ ወንጀል መፈፀማቸዉን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።ይሁንና ባሁኑ ወቅት የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሟል ለማለት በቂ መረጃ እንደሌለዉ ድርጅቱ ገልፆል።
Tweet media one
37
46
139
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
በኢትዮጵያ ግጭት የተሳተፉ የተለያዩ ወገኖች የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ብለው እንደሚያምኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጥሰት መርማሪዎች ዛሬ ገለጹ።በትግራይ ከሚፈጸሙ ወንጀሎች በስተጀርባ የመንግሥት እጅ እንዳለም ተናግረዋል።
Tweet media one
35
96
138
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ሰባት የቤተ ክርስትያን መዘምራን ሲያገለግሉ ባመሹበት የቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስትያን አንድ ክፍል ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን በምሥራቅ ሸዋ ዞን የአዳማ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ። ሟቾቹ እዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች የሆኑ ስድስት ሴቶችና 1 ወንድ ናቸው።
Tweet media one
42
23
131
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
«ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት» ከ31.4 ሚሊዮን ብር በላይ ዛሬ ለወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አስረከበ። ገንዘቡ በጌድዮ ጉጅ ዞን ግጭት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስና መልሶ ለማቋቋም የሚውል ነው ተብሏል። (ቪዲዮ፦ሰለሞን ሙጬ)
10
23
139
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
«የወርቅ ሜዳሊያውን ከእኔ ይልቅ ለጀግኒቷ እናቴ ይሸልሙልኝ» ዛሬ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማዕረግ (3.76) የሕክምና ዶክተሬቱን ያጠናቀቀው ዶክተር ብዙአየሁ አሰፋና እናቱ ለ @dw_amharic ከተናገሩት ባጭሩ። (የቪዲዮ ዘገባ፦ ሸዋንግዛው ወጋየሁ)
9
25
137
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የኢትዮጵያ መንግስትና ተባባሪዎቹ ኃይላት የሽረ ከተማን ከህወሐት እጅ አስለቀቁ።ሽረና አካባቢዋ ከፍተኛ ዉጊያ ሲደረግባቸዉ ነበር።የሕወሓት የጦር ዕዝ እንዳስታወቀዉ የኢትዮጵያ መንግስትና ተባባሪዎቹ «ሽረ ገብተዋል» ዲፕሎማቶችም አረጋግጠዋል።
Tweet media one
21
14
132
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ትግራይ መቀሌ በምርጫው ዋዜማ ቪዲዮ፦ ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
17
16
124
@dw_amharic
DW Amharic
6 years
የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀድሞዋ የተቃዋሚ ፓርቲ የአንድነት ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሠብሳቢ አድርጎ ሾመ።ምክር ቤቱ ሹመቱን ያፀደቀዉ በ4 ተቃዉሞ በ3 ተአቅቦ እና በአብላጫ የድጋፍ ድምፅ ነዉ።
Tweet media one
2
16
125
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የዶይቸ ቬለ (DW) ጋዜጠኛ ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ ባደረበት ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ዶይቸ ቬለን ለረዥም ዓመታት ያገለገለው ጋዜጠኛ ጌታቸው ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ጣቢያው እና ባልደረኖቹ ጥልቅ ሃዘናቸውን ይገልፃሉ።
Tweet media one
37
15
122
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን ከዛሬ ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ጸሎትና ምህላ አወጀች።
Tweet media one
1
19
124
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የተ.መ.ድ. በትግራይ ለሚኖሩ ዜጎች የቴሌኮምዩንኬሽን አገልግሎት፣ የምግብ፣ የመድሐኒት እና የነዳጅ አቅርቦት እንዲጀመር ጠየቀ። 👇
9
40
114
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለ5 አመታት ኢትዮጵያን ለመምራት ቃለ-መሐላ ፈጸሙ። ብልጽግና ፓርቲ ከመጋቢት 2010 ዓ.ም ጀምሮ በጠቅላይ ምኒስትርነት ኢትዮጵያን በመምራት ላይ የሚገኙትን ዐቢይ አሕመድ በእጩነት አቅርቦ ሹመታቸው በቀጥታ ጸድቋል
Tweet media one
11
31
123
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
በሰበታ መኖሪያ ቤት ከፈረሰባቸው መካከል አንዷ የሆነችው ሐድራ ሸረፈዲን ትናገራለች
15
71
117
@dw_amharic
DW Amharic
1 year
የሰሜን ሸዋው ጥቃትና ግድያ ጥቁር ጠባሳ ሳይሽር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ላይ በሻሸመኔ «ፖሊስ በወሰደው ጭካኔ በሞላበት ሁኔታ የአደባባይ የግድያ ወንጀል» እንደተፈጸመ ሲኖዶስ ገልጧል። ሳምንታዊ ውይይት፦
6
53
119
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
በወለጋ ጊምቢ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ የተፈፀመውን ጅምላ ጭፍጨፋ የሚያወግዙ ሰልፎችና ተቃውሞወች ዛሬ በባሕር ዳር የተለያዩ ተቋማት ተካሂደ፡፡
Tweet media one
8
34
114
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
አዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ የሚገኘው እድሜ ጠገቡ በቅርስነት የተመዘገበው አንበሳ መድኃኒት ቤት በር ተሰብሮ ዕቃዎች እንዲወጡ ተደረገ (ቪዲዮ) ቪዲዮ፦ ሰለሞን ሙጬ፤ ለዶይቸ ቬለ (DW)ከአዲስ አበባ
32
69
110
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ከዓለም አቀፉ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጥምረት የደረጃ 1 ዕውቅና የተሰጠው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዕውቅናው ሥራውን በገለልተኝነትና በታማኝነት እንዲሠራ የበለጠ እንደሚያተጋው አመለከተ።
Tweet media one
8
34
112
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
በኦሮሚያ ክልል ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ አገምሳ ከተማ ትናንት ከማለዳ ጀምሮ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 55 ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ።
Tweet media one
26
112
109
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
ሰበር ዜና፦ ኢትዮጵያ የታላቁ የኅዳሴ ግድብ «የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ ለማዘጋጀት የሚደረገው ድርድር ተጠናቋል በሚል» አሜሪካ ያወጣችውን መግለጫ ውድቅ አደረገች።
Tweet media one
5
23
110
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
የኢትዮጵያ አርበኞች ከአምስት ዓመታት ዉጊያ በኋላ የኢጣሊያ ወራሪ ጦርን ድር ያደረጉበት 78ኛ ዓመት በዓል ዛሬ ተከብሮ ዋለ።
5
23
107
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የፀጥታዉ ምክር ቤት ስለ ሕዳሴ ግድብ ዛሬ የሚያደርገዉን ዉይይት ኢትዮጵያ ተቃወመች።ዉጉሚ ደመቀ ለዐባይ ተፋሰስ ሐገራት ዲፕሎማቶች እንደነገሩት ምክር ቤቱ ጉዳዩን የመመልከት ኃላፊነት የለዉም።ምክር ቤቱ እንዲወያይ የጠየቀችዉ ቱኒዚያ ናት
Tweet media one
5
23
103
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የአፋር ክልል ሕዝብ ለረሐብ አደጋ መጋለጡን የአፋር ሕዝብ ፓርቲ አስታወቀ።የአፋር ክልል ልዩልዩ ኃይላት ከሕወሓት ጋር በገጠሙት ዉጊያ በሺሕ የሚቆጠር ሰዉ ሞቷል።ከ350 ሺሕ ሕዝብ ከማፈናቀሉም በላይ ለከፋ የምግብ እጥረት አጋልጧል
Tweet media one
4
59
107
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
ቪዲዮ፦ የኢትዮጵያ ጦር የሶማሊያ ወራሪ ኃይልን በጦርነት ያሸነፈበት የካራማራ ድል ዛሬ በጥቂት የአዲስ አበባ ወጣቶች ታስቦ ውሏል። ወጣቶቹ በኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት ሐውልት በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። (ቪዲዮ- ሰለሞን ሙጬ )
4
28
101
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ከአንድ ወር በፊት ሚያዚያ 12/2013 ዓ.ም ተፈፀመ ተብሎ የተዘገበው የመርዛማ ጋዝ ጥቃት ሊሆን ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል ነው ሲል አስተባብሏል።
Tweet media one
17
31
98
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው ዓመት በዲፕሎማሲያው መስክ ትልልቅ ችግሮችን ብትጋፈጥም ስኬቶችም ተገኝተዋል ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።
Tweet media one
3
28
98
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም. በጅግጅጋ ከተማ በተፈጸመ ጥቃት ከተቃጠሉ አራት አብያተ ክርስትያናት በሕዝብ ድጋፍ መልሶ በመገንባት ላይ የሚገኘው የኪዳነ-ምህረት ቤተክርስትያን ግንባታ ሒደት (ቪዲዮ፦ መሳይ ተክሉ)
0
11
105
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
የሶማሌ ክልል መንግሥት ዛሬ ሲመሰረት አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ፕሬዝደንት፣ አቶ ኢብራሒም ኡስማን ምክትል ፕሬዝደንት ሆነዋል። ለክልሉ ምክር ቤት ወይዘሮ አያን አብዲ አፈ-ጉባኤ አቶ ኢብራሒም ሐሰን አሊ ምክትል አፈ-ጉባኤ ሆነዋል
Tweet media one
6
18
101
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ መንግሥት አማጽያንን ለመዋጋት የቱርክ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መጠቀሙን የሚያመለክቱ መረጃዎች እንዳሏቸው እየገለጹ ነው።
Tweet media one
173
15
101
@dw_amharic
DW Amharic
6 years
ታዋቂዋ ፖለቲከኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ቤተሰቦቻቸው በሚኖሩበት በአዲስ አበባው ፈረንሳይ ለጋሲዮን የተረገላቸዉ ደማቅ አቀባበል በከፊል። «ቪዲዮ :- በዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር»
2
20
102
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር በኢትዮጵያ ሲያደርጉ የነበሩትን የአራት ቀናት ጉብኝት አጠናቅቀዋል። ፕሬዝዳንት ሽታይንማየር ከአዲስ አበባ ከመነሳታቸው ቀደም ብሎ ተከታዩን ቃለ-ምልልስ ለጀርመን የብዙሃን መገናኛዎች ሰጥተዋል።
6
12
98
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
«ያለ ወንድማማችነት ዴሞክራሲ በጭንጫ የሚዘራ ዘር ነው»ሲሉ የኢ/ጠ/ሚ ዶክተር ዐብይ አሕመድ ገለፁ።እሳቸው እንዳሉት ስለ ዴሞክራሲ ግንባታ ሲታሰብ ከነጻነትና ከእኩልነት ባሻገር የተዘነጋው የወንድማማችነት ዕሴት ትኩረት ሊያገኝ ይገባል።
Tweet media one
36
11
98
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
ሕወሓት ይቆጣጠራቸዉ በነበሩት አካባቢዎች የጅምላ መቃብር መገኘቱን የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ።የጠቅላይ ሚንስትር የፕሬስ ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ዛሬ «አሸባሪ» ያሉት ሕወሓት ሰዎችን በጅምላ ገድሏል፣ ሴቶችን ደፍሯል፤ ሐብት ንብረት አዉድሟልም።
Tweet media one
6
58
100
@dw_amharic
DW Amharic
3 years
በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የሚመሰክሩ ምስክሮች ከመጋረጃ ጀርባ ይሰሙ መባሉ ውድቅ ተደረገ። «ምንም አይነት ከመጋረጃ ጀርባም ሆነ በዝግ የሚደረግ ምስክርነት አሰጣጥ አይኖርም።»
Tweet media one
2
10
97
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
በትግራይ በሴቶች ላይ የሚፈፀመውን ፆታዊ ጥቃት የሚያወግዝ የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬ በመቐለ ተካሄደ። በሰልፉ ላይ ፆታዊ ጥቃትን የሚያወግዙ መፈክሮች ቀርበዋል፤ አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጥቃቶችም በጥበባዊ መንገድ ተንፀባርቀዋል። 👉
Tweet media one
4
30
101
@dw_amharic
DW Amharic
6 years
ታዋቂዋ ፖለቲከኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ይኖሩበት ከነበረው አሜሪካ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ቤተሰቦቻቸው በሚኖሩበት በአዲስ አበባው ፈረንሳይ ለጋሲዮን ሰፈር ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ጠብቋቸዋል። (በዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር)
Tweet media one
Tweet media two
Tweet media three
Tweet media four
2
27
100
@dw_amharic
DW Amharic
5 years
የአጣዬ እና አካባቢውን ሰላም እያወኩ ያሉት “የተደራጁ ኃይሎች” መሆናቸው ሲገለጽ ቢቆይም የሰሜን ሸዋ ዞን የአስተዳደር እና ፀጥታ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ግን “ማሽሞንሞን አያስፈልግም፤ ኦነግ ነው” ሲሉ ወንጅለዋል።
Tweet media one
10
38
91
@dw_amharic
DW Amharic
6 years
አፄ ኃይለ ሥላሴ፣ «ባለራዕዩ» ንጉሥ በጎርጎሪዮሳዊው 1923 ዓ/ም ኢትዮጵያ የሊግ ኦፍ ኔሽንን አባል በመሆን ከአፍሪቃ የመጀመሪያዋ ናት። ይህ እውን የሆነው አህጉሪቱ በአውሮጳ ቅኝ አገዛዝ ስር ሆና ግንኙነቱም እኩል ባልነበረበት ወቅት ነው። #ARAMH
1
40
96
@dw_amharic
DW Amharic
2 years
«ኦሮሚያ ያለውን አለመረጋጋት መንግስት በነካ እጁ ቢያስብበት» ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
Tweet media one
26
12
97
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
«በትግራይ ሕዝብ ክፉ ነገር እንዲደርስ አንፈልግም።ክፉ የሚያደርጉትንም አንታገሥም» የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት ://www.facebook.com/dw.amharic/photos/a.507141705985597/3925445674155166/
Tweet media one
14
5
94
@dw_amharic
DW Amharic
8 months
የኢትዮጵያ መንግስት ገላን ክፍለ ከተማ ካሰፈራቸዉ ሰዎች በተስቦ በሽታ ቢያንስ 3ቱ መሞታቸዉ፣ 3 በጠና፣190 በቀላሉ መታመማቸዉን ኢሰመኮ አረጋገጠ። ሰዎቹ የሰፈሩት በቂ መኝታ፣ አልባሳት፣ ዉኃ፣ ንፁሕ ዓየርና ፀሐይ በማይገባበት መጋዘን ነዉ።
Tweet media one
18
85
96
@dw_amharic
DW Amharic
4 years
የህወሓት የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚዓብሔር ከጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ካቢኔ ተሰናበቱ፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስትር የነበሩት ፈትለወርቅ ተሽረዉ አቶ መላኩ አለበል ተሾመዋል👇
Tweet media one
15
22
92