የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን በሚደግፍ ሰልፍ ላይ ድምጻዊ ታሪኩ "ሽምግልና ይሻላል" ብሏል
ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ድጋፍ ለማሳየት በተካሔደ ሰልፍ ድምጻዊ ታሪኩ ጋንካሲ "ሽምግልና ይሻላል" የሚል ጥሪ አቀረበ። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ታዳሚ በተገኘበት ሰልፍ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "እንነሳ፤ የመከላከያ ሠራዊታችንን እንቀላቀላቸው፤ አብረናቸው እንቁም" የሚል ጥሪ አቅርበዋል።